| የአውሮፓ ህብረት የታዛቢዎች ቡድን የምርጫው ሂደት ከመቋጨቱ በፊት መግለጫ አዘጋጅ |
|
|
|
| Written by solomon | |||
| Saturday, 22 May 2010 07:38 | |||
|
በኢትዮጵያ ለአራተኛ ጊዜ በመካሄድ ላይ የሚገኘው ምርጫ 2002 ለመታዘብ የመጣው የአውሮፓ ህብረት የታዛቢዎች ቡድን የምርጫው ሂደት የሚያጣጥል መግለጫ ማዘጋጀቱን የውስጥ አዋቂ ምንጮች ገለፁ።
ቡድኑ ይህንን መግለጫ ያዘጋጀው የምርጫው ሂደት ከመጠናቀቁ በፊት መሆኑ ቡድኑ የምርጫውን ሂደት ነፃ፣ ሰላማዊ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ መሆን ላይ ቅድመ ድምዳሜ መያዙን ምንጮቹ አክለው ገልፀዋል።
እንደምንጮቹ አገላለፅ የአውሮፓ ህብረት የታዛቢዎች ቡድን የምርጫውን ሂደት ሳይጠናቀቅ እንዲህ አይነቱ መግለጫ ለማውጣት መዘጋጀቱ ቡድኑ ለኢትዮጵያ ህዝብ ድምጽ ክብር መስጠት ላይ ያለውን አቋም ጥያቄ ውስጥ ያስገባል።
በሌላ በኩል ደግሞ አንዳንድ የቡድኑ አባላት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ የሚመሩት ኢህአዴግ የኢትዮጵያ ህዝብ ይሁንታ አግኝቶ ስልጣን መያዙ እንደሚደግፉ ለማወቅ ተችሏል።
|
Add your comment
ADD
Comments, category: "amharic"
- የአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጆች ሕትመቱን አቋርጠው ተሰወሩ (4)
- እኛ ካላሸነፍን ምርጫው መጭበርበሩ ይታወቃል ሲሉ የአንድነት አመራሮች አስታወቁ (2)
- አቶ ስዬ አብርሃ መንታ መንገድ ላይ መቆማቸው ታወቀ (1)
- ከአፄው ስርዓት ጋር የሚመሳሰል የምርጫ ቅስቀሳ በተምቤን ተጀመረ (1)
- ኢትዮጵያ ግብረ-ሰዶም ባለመፍቀዷና ግልገል ጊቤን በማልማቷ ሁማን ራይትስ ዎች ከሰሰ፤ አቶ ገብሩ አስራትና አቶ ቡልቻ ደመቅሳ በምንጭነት ተጠቅሰዋል (1)
- የኢ/ጉ/ገ/ ባለሥልጣን 6 ህገ ወጥ ነጋዴዎች ወደ ህግ ማቅረቡን አስታወቀ (1)











