| ሩሢያ ሂትለርን ድል የተመታበት 65ኛ ዓመት |
|
|
|
| Written by solomon | |||
| Sunday, 09 May 2010 16:09 | |||
|
ሩሢያ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት በናዚው አዶልፍ ሂትለር ላይ ድል የተቀዳጀችበትን 65ኛ ዓመት በሞስኮ ቀይ አደባባይ በተካሄደ የደመቀ ወታደራዊ ሰልፍ አከበረች። ከአሥር ሺህ የሚበልጡ ወታደሮች በተሳተፉበት የድል ሰልፍ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የፖላንድ፣ የፈረንሣይ፣ የብሪታኒያና የአሜሪካ ሠራዊት ባልደረቦችም ተካፍለዋል። ሰልፉ ከዚሁ ሌላ ከ 120 በሚበልጡ የጦር አውሮፕላኖች፣ ሄሊኮፕተሮች፣ ታንኮችና ታሪካዊ የጦር መሣሪያዎች የታጀበ ነበር። በሩሢያው ፕሬዚደንት በዲሚትሪይ ሜድቬቭ ግብዣ በቀዩ አደባባይ ስነ-ስርዓት ላይ ከተገኙት የመንግሥታት መሪዎች መካከል የጀርመኗ ቻንስለር አንጌላ ሜርክልም አንዷ ናቸው። አንጌላ ሜርክል ግብዣውን ሩሢያና ጀርመን ከታሪክ ተምረው በሰላምና በወዳጅነት መኖር መቻላቸውን የሚያመለክት ነው ብለዋል።
|
Add your comment
ADD
Comments, category: "amharic"
- የአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጆች ሕትመቱን አቋርጠው ተሰወሩ (4)
- እኛ ካላሸነፍን ምርጫው መጭበርበሩ ይታወቃል ሲሉ የአንድነት አመራሮች አስታወቁ (2)
- አቶ ስዬ አብርሃ መንታ መንገድ ላይ መቆማቸው ታወቀ (1)
- ከአፄው ስርዓት ጋር የሚመሳሰል የምርጫ ቅስቀሳ በተምቤን ተጀመረ (1)
- ኢትዮጵያ ግብረ-ሰዶም ባለመፍቀዷና ግልገል ጊቤን በማልማቷ ሁማን ራይትስ ዎች ከሰሰ፤ አቶ ገብሩ አስራትና አቶ ቡልቻ ደመቅሳ በምንጭነት ተጠቅሰዋል (1)
- የኢ/ጉ/ገ/ ባለሥልጣን 6 ህገ ወጥ ነጋዴዎች ወደ ህግ ማቅረቡን አስታወቀ (1)











